ስትራቴጂካዊ ቅድሚያ የሚሰጣቸው ነገሮች።

የ OEO የሕግ አውጪ ተልዕኮ ዕድል ክፍተቶችን ለመቀነስ ነው። የስትራቴጂክ እቅዳችን ውስን የግጭት አፈታት ሀብቶቻችንን ለምሳሌ መደበኛ ያልሆነ ሽምግልና እና ስልጠናን በሚከተሉት K-12 ተማሪዎች ላይ በማተኮር የእድል ክፍተቱን ለመቀነስ ቅድሚያ ይሰጣል፦

  • በከፊል የትምህርት ቀናት የሚያገኙ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎችን ጨምሮ ከትምህርት ውጪ የሆኑ
  • ቀለም ያላቸው፣ ጥቁሮች ወይም የአገሬው ተወላጅ የሆኑ 
  • የቤት እጦት እያጋጠማቸው ያሉ
  • በዘመድ ወይም በማደጎ ውስጥ ያሉ 
  • በወጣት ፍትህ ወይም በወጣት ማገገሚያ ስርዓቶች ውስጥ የተሳተፉ
  • አዲስ መጤ፣ ስደተኛ፣ ጥገኝነት ፈላጊ ወይም ጊዜያዊ ስደተኛ፣ ወይም የመጀመሪያ ቋንቋቸው እንግሊዘኛ ያልሆኑ ተማሪዎች ወይም ቤተሰቦች
  • በተጠናከሩ አገልግሎቶች የተጠቀለለ (WISe) ወይም የልጆች የረጅም ጊዜ የተኝቶ ታካሚ ፕሮግራሞች (CLIP) ድጋፎችን እየተቀበሉ ያሉ፣ ወይም
  • ፆታ የቀየሩ ወይ ፆታ የሌላቸው ወጣቶች